ምክር ቤቱ
1.
ህገ-መንግስትን
ይተረጉማል፣
2.
የሕገ-መንግስት ጉዳዮች አጣሪ ጉባዔን ያደራጃል፣
3.
የብሔሮች ብሔረሰቦችና ሕዝቦች የራስን እድል በራስ የመወሰን እስከ መገንጠል መብት በተመለከተ
በሚነሱ ጥያቄዎች ላይ በሕገ-መንግሥቱ
መሠረት ይወሰናል፣
4.
በሕገ-መንግሥቱ የተደነገገው በሕዝቦች እኩልነትና በሕዝቦች መፈቃቀድ ላይ የተመሠረተ አንድነት
ሥር እንዲሰድና እንዲዳብር ያደርጋል፣
5.
በክልሎች መካከል ለሚነሱ አለመግባባቶች መፍትሔ ይፈልጋል፣
6.
የክልሎችና የፌዴራል መንግሥት የጋራ ተብለው የተመደቡ ገቢዎች በሁለቱ መካከል የሚከፋፈሉበትን
እንዲሁም የፌዴሪል መንግሥት ለክልሉች ድጐማ የሚሰጥበትን ቀመር ይወስናል፣
7.
በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሕግ ሊወጣላቸው የሚገቡ የፍትሐብሔር ጉዳዮችን ይለያል፣
8.
ማንኛውም ክልል የፌዴራል ሕገ-መንግሥቱን በመጣስ ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱን አደጋ ላይ የጣለ
እንደሆነ የፌዴራል መንግሥት ጣልቃ እንዲገባ ያዛል፣
9.
በሕገ-መንግሥቱ 1)3/5 መሠረት የምርጫ ቦርድ በሚያቀርብለት ረቂቅ የምርጫ ክልሎች አከላለልን
ይወስናል፣
10. በሕገ-መንግሥቱ አንቀጽ (፱ መሠረት ለፌዴራል ወይም ለክልል መንግሥታት ተለይተው ባልተሰጡ
ታክስና ግብር የመጣል ሥልጣኖች ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጋር በጋራ ይወስናል፣
11. በሕገ-መንግሥቱ አንቀጽ &/፪ ከሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጋር በሚደረግ የጋራ ስብሰባ የአገሪቱን
ፕሬዝዳንት ይመርጣል፣
12. በሕገ-መንግሥቱ አንቀጽ ()) ንዑስ አንቀጽ (፩) እና (፪) በተገለፀው መሠረት ሕገመንግሥቱን በማሻሻል
ሂደት ይሳተፋል፣
13. በሥልጣኑ ሥር በሚካተቱ ጉዳዮች ላይ ከሌሉች ጋር በመተባበር ትምህርትና ሥልጠና ይሰጣል
እንደአስፈላጊነቱም ጥናትና ምርምር ይካሂዳል፣
14. የምክር ቤቱ ቋሚና ጊዜያዊ ኮሚቴዎች ያቋቁማል፣
15. የራሱን አፈ-ጉባዔና ምክትል አፈ-ጉባዔ ይመርጣል፡፡
|